ዘርአዳዊት ዘ-ኢትዮጵያ
ታሪካዊት የኢትዮጵያ ጠላት ሀገረ እንግሊዝ ፡ በመዝገቨ ቃላት ማኅደርዋ ረሀብ ወይም ድርቅ ለሚለው ቃል ፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ እንደ ምሳሌ ጠቅሳታለች። ኢትዮጵያ በአብዛኛው የዓለማችን ማኅበረሰብም በረሀብና በድርቅ ብቻ ትታወቃለች። ይህ እንዲሆንም በዲያብሎስ አገልጋዮች ምዕራባውያን ፡ ሆን ተብሎ የተደረገ ነው። ይህም ከጥንት ጀምሮ የእግዚአብሔር ሀገር በመሆንዋ ያደረባቸው ጥላቻ የሚወጡበት ሆኗል። ድንቅ የሆነው “የዓድዋ ድል” ቪክቶሪ (Victory) ለሚለው ቃል
፡ ምሳሌ ማድረግ አይፈልጉም ፤ ምክንያቱም ድል የተደረገው አካል ማን እንደሆነ ፡ ለዓለም ህዝብ ግልጽ ነው።
በሰው ልጅ ታሪክ መዝገብ ውስጥ ፡ ከፍተኛና ዘግናኝ የረሀብና ድርቅ ሁኔታዎች ተከስተው አልፈዋል ፤ አሁንም እየተከሰቱ ነው። እስከ አሁን በአስከፊነታቸው ፡ ከተመዘገቡት ውስጥም በኢትዮጵያ የተከሰተው ድርቅና ረሀብ ግን እስከ ፲ኛ ደረጃ ውስጥ አይገኝም ፤ ቢሆንም ምዕራባውያን ፲፱፻፸፯ ዓ.ም በሀገራችን ኢትዮጵያ የተከሰተው መጥፎ ሁኔታ ፡ በማጋነን የኢትዮጵያ ስም ለማጥፋት ተጠቅመዉበታል።
ከ ፩ እስከ
፲ የተመዘገቡ ፡ አስከፊ ፡ የረሀብና ድርቅ
ክስተቶች እንመልከት ፦
፲ኛ. ታላቁ የሀገረ አየርላንድ ድርቅ ፡ ከ ፩ ሚልዮን በላይ ሰው የሞተበት።
፱ኛ. የቬትናም ድርቅ ፻፱፵፭ ፪ ሚልዮን ህዝብ የሞተበት ፲፱፻፵፭ !
፰ኛ. የሰሜን ኮርያ ድርቅ ፫ ሚልዮን ህዝብ የሞተበት !
፯ኛ. የሩስያ ድርቅ ፻፱ ፭ ሚልዮን ህዝብ የሞተበት ፲፱፻፳፩!
፮ኛ.የቤንጋል ድርቅ ፯ ሚልዮን ህዝብ የሞተበት ፲፱፻፵፫ !
፭ኛ.የቤንጋል ድርቅ ፲ ሚልዮን ህዝብ የሞተበት ፲፯፻፸ !
፬ኛ.የሶቬት ድርቅ ፲ ሚልዮን ህዝብ የሞተበት ፲፱፻፴፪ - ፲፱፻፴፫ !
፫ኛ. የቻሊሳ ድርቅ ፲፩ ሚልዮን ህዝብ የሞተበት !
፪ኛ. የቻይና ድርቅ ፳፭ ሚልዮን ህዝብ የሞተበት ፲፱፻፯ !
፩ኛ. የታላቋ ቻይና ድርቅ ፵፫ ሚልዮን ህዝብ የሞተበት !
ታድያ
ለምን ኢትዮጵያ ፡ በምዕራባውያን ዘንድ ፡ የረሀብና ድርቅ ተምሣሌት ልትሆን ቻለች ፧ መልሱ ግልጽ ይመስለኛል።
ኅሙስ ጥቅምት 4, 2008 ዓ.ም










No comments:
Post a Comment