ዘርአዳዊት ዘ-ኢትዮጵያ
የእግር ኳስ ዓለም ዋንጫ ፡ ሊጀመር ጥቂት ቀናት ቀርቶታል። በአሁኑ ጊዜ ፡ እግር ኳስ ፡ ለኢትዮጵያውያን ፡ ማንነታችን እያስረሳን ይገኛል። ፳፬ ሰዓት ፡ የምዕራባውያን ፡ እግር ኳስ ፡ የሚመግቡን መገናኛ ብዙሃንና ጋዜጠኞች ፡ እንደ አሸን በበዙበት ፡ ስለ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊ ማንነት ፡ ደፍሮ ለመናገርና ለማስተማር የሚሞክሩት መርሐ ግብሮች ግን ጥቂትና ዘላቂት የሌላቸው ናቸው። የምዕራባውያን እግር ኳስ የሚደሰኩርልን አካላት ፡ በተለይ የወጣቱ አዕምሮ በመቆጣጠር ፡ እግር ኳስ ፡ ከመዝናኛነት አልፎ ትልቁ የህይወታችን ክፍል በማድረግ ፡ ትኩረት ልንሰጥበት
የሚገባን ጉዳዮች ፡ ያለ በቂ ትኩረት እንድናልፋቸውና ምዕራባውያን ላዘጋጁልን የባርነት ወጥመድ ፡ተገዢ እንድንሆን እያደረገ ይገኛል።
በአውሮፓና ደቡብ አሜሪካ ውስጥ ፡ የእግር ኳስ ፡ ጨዋታዎች በኢሉሚናቲ ቁጥጥር ሥር ከወደቁ ፡ አንድ ክፍለ ዘመን ገደማ ሆኖታል። ከሣምንት ፭ ወይም ፮
ቀናት በመንግሥት ሥራ የባርነት ሥርዓት ውስጥ ፡ ለቆዩ ሰራተኞች (ባርያዎች) ፮ኛው ወይም ፯ኛው ቀናቸው እግርኳስ እንዲመለከቱ በተለያዩ መንገዶች ተጽዕኖ በማድረግ ፤ ስለ ሚደግፉት ቡድን መረጃ በብዛት እንዲያገኙና በጨዋታው ውስጥ ዳኛው ስለወስናቸው ውሳኔዎችና ሌላ ተያያዠ ጉዳዮች
በማንሳት ፡ ቀጣይ ፭
ወይም ፮ የሥራ ቀናት ስለነዚ ነገሮች እንዲያወሩና እንዲያስቡ በማድረግ ፡ ሰራተኛው ወይም በጠቅላላ የዓለም ህዝብ ፡ ለህይወቱ ወሳኝ ስለሆኑ ነገሮች እንዳያስብ ፡ ዘላለም በባርነት እንዲኖር ሊያደርጉት ችለዋል።
በቢልዮን የሚቆጠር ህዝብ ፡ ሴረኞች ባሴሩት ጦርነት ያለ ኃጥያቱ ፡ በተለይ ህጻናት ጭንቅ ውስጥ ባሉበትና እንዲሁም ብዙ የዓለማችን ህዝብ ፡ ዕለታዊው የምግብ ፍላጎቱ ሟሟላት ሳይችል ፡ በረሀብ በሚሞትበት ዓለም በቢልዮን የሚቆጠር ገንዘብ በማውጣት ፡ የእግርኳስ ድግስ በማዘጋጀት ፡ የዓለም ህዝብ ማደንዘዝ ፡ ሰይጣናዊ ሥራ እንጂ ሌላ ምንም ሊሆን አይችልም።
ሰኞ ሰኔ 4, 2010 ዓ.ም
No comments:
Post a Comment