EAR

አዲስ ነገር

Friday, 22 April 2016

የባንክ ስርዓት - ዘመናዊ ባርነት

ዘርአዳዊት -አቢሲንያ



የዘመኑ ሃይለ መንፈስ ያስተዋለ ሰው የአውሬው 666 ሴራ ወዴት እያመራ እንደሆነ መገንዘብ አይከብደዉም።የሰላቢ እጆች(ኢሉሚናቲ) ዋነኛዋ የሴራ ማዳረሻ ሃገራችን ኢትዮጵያ ነች።የ አውሬው 666 የመጨረሻ ዕቅድና ግብም አንድ የዓለም መንግሥት በመመሥረት የሰው ልጅን ቁጥር ወደ 500 ሚልዮን በተለያዩ ሴራዎች በመቀነስ የድያብሎስ ባርያ በማድረግ እስከ ዓለም ፍጻሜ ማድረስ ነው።አንድ የዓለም መንግስት ላይ ለመድረስ ሥስት ደረጃዎች ይከተላሉ።

፩.የዓለም ሃይማኖቶች በማጣመር አንድ ሃይማኖት መመሥረት(የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን ዋናዋ የሴራ ግባቸው ነች።)
፪.አንድ የአለማችን የመገባበያ ገንዘብ ማውጣት(የአውሮፓ ሃገሮች ዩሮ የጋራ መገባባያ ገንዘባቸው መሆኑ አስታውስ)
፫.የመጨረሻው ዕቅድ የሆነው አንድ የዓለም መንግስት መመሥረት

የዚህ ጽሑፍ ትኩረትም ፪ኛው ደረጃ ላይ ይሆናል።ይህም ሰሞኑን የሃገራችን ባንኮች የጋራ የኤቲኤም ካርድ ለመጠቀም የወሰኑበት ሁኔታ ላይ መሠረት አርገን ቀጣዩ አቅጣጫስ ምን ሊሆን እንደሚችን እናያለን ማለት ነው።
ገንዘብ ምናባዊ የሆነ የሰው ልጅን ለመቆጣጠር በሚያስችል መልኩ በተዘረጉ የባንክ ስርዓቶች የሚንቀሳቀስ መሣርያ ነው። የምስጥር ማህበራት በተቆጣጠሩት የዓለም የባንክ ስርዓት  በሰው ልጅ ላይ የሃብት ክፍፍል በመፍጠር ድሃና ሃብታም ብለው በመለየት የሰው ልጅን በገንዘን ምክንያት በቁጥጥራቸው(ባርያ በማድረግ) ስር ለማዋል የፈጠሩት ሴራ ነው።

የአውሬው 666 ፈረሶች የሆኑት  እነዚህ የምስጥር ማህበረት የተቆጣጠርዋቸው የባንክ ስርዓቶችም በዓለም ላይ አንድ ዓይነት ማለትም የካርድ መገበያይ እንዲኖር እየሰሩ ነው።ይህ ማለትም የወረቀት የገንዘብ ኖት በማስቀረት በአንድ ጣብያ ብቻ በመሆን በኮምፒተር በሚቆጣጠሩት የካርድ አገልግሎት ቀስ በቀስ አለም አቀፋዊ በማድረግ የሰው ልጅን ባርያ ማድረግ ዓላማቸው ነው።የኛ ባንኮች ጉዞም ወደዚህ አቅጣጫ ይሆናል።
የመጽሓፍ ቅዱስ ክፍል በሆነው የየውሓንስ ራዕይ መጽሓፍም እንዲህ የሚል ቃል ይገኛል።

‹‹ሁለተኛው አውሬ ታናናሾችም ሆኑ አገልጋዮች ሁሉም በቀኝ እጃቸው ወይም በግንባራቸው ላይ ምልክት እንዲያደርጉ አስገደዳቸው።በዚህ ዐይነት የአውሬው ስም የሆነው ምልክት ወይም የስሙ ቁጥር የሌለው ማንም ሰው መግዛትም ሆነ መሸጥ አይችልም።››--ምዕራፍ 13 ቁጥር 16-17  


 ሚያዝያ 12,2008