ዘርአዳዊት ዘ-ኢትዮጵያ
የካቶሊክ ርዕሰ ጳጳስ ፍራንሲስ የፍሪማሶን የሰይጣን አምልኮ መግባብያ የሆነው የእጅ ምልክት ሲያሳዩ
የመጽሓፈ ገጽ (facebook) ህዋ ሰሌዳ ካስተዋወቁኝ ሰዎች መካከል አንዱ በብዕር ስሙ የምናውቀው አሌክስ አብርሃም ነው።የአሌክስ አብርሃም ጽሑፎች አብዛኛዎቹ ትኩረቴ ባይስቡትም በተለያዩ ጎጂ ሱሶች ላይ ያለው አቋም ግን ቀንደኛ ደጋፊው ነኝ።አሌክስ አብርሃም በመጽሓፈ ገጽ ብዙ አንባቢ እንዳለዉም አውቃለው።በዚህ ምክንያትም ነው ይህንን ጽሑፍ ለመጻፍ የፈለኩት።ብዙ ተከታይ ያላቸው ሰዎች የሚጽፉት፣ የሚናገሩት በጠቅላላ የሚያደርጉት ነገር በብዙ ሰዎች ዘንድ ሁሌ እንደ ትክክል የመቆጠር እድሉ የሰፋ ነው።በተለይ የራሱ ጥናትና ምርምር ሳያደርግ የሚቀርብለትን ማነኛውም መረጃ ሳያላምጥ ለሚውጥ ማህበረሰብ።
አሌክስ አብርሃም በተደጋጋሚ ጊዜ ስለ ሰላቢ-እጆች (ኢሉሚናቲ) በሚወጡ መረጃዎች ላይ በመሳለቅና በመቀለድ እውነተኝነታቸውን ለመደበቅ ሲሞክር ስለአየሁት ነው።በዚህ አጋጣሚ ማለት የምፈልገው አንድ ሰው ሁሉም ነገር ሊያውቅ አይቻለዉምና የማናውቀው ወይም ያልገባን ነገር ለመረዳት በመጠየቅና የግል ጥናት በማድረግ ለማወቅ መሞከር አለብን እንጂ ስላልገባን መሳለቅና መቀለድ የለብንም።ይባስ ብሎም ሰዎችን ማሳሳት የለብንም።
ሰሞኑን አሌክስ አብርሃም "አሁን አሁን በቃ በየቦታው ሰው የሆነ ምልክት ካሳየ ኢሉሙናቲ ነው ምናምን ነው ይባላል።አሁን መቸ ለት ከወዳጀ ጋር ቀበሌ ሄድንና ሴትዮዋ የሆነ የእጅ ምልክት ስታሳይ አብሮኝ የነበረው ወዳጀ በቃ ሁሉም አባል ናቸው ማለት ነው እያለ የቁም ቅዠቱን ጀመረ......"እያለ እያለ ይቀጥላል። ይህም ብዙዎች የኢሉሚናቲ አገልጋዮችና አባላት የሚያሳይዋቸው ምልክቶች ምንም እንዳልሆኑ ለመግለጽ
ነው። አሌክስ አልገባህም እና እንዲገባህ የግልህ ጥናት አድርግ እልሃለው።አለበለዝያ እውነታው ለመደበቅ ሆን ብለው የተሳሳተ መረጃ
በመልቀቅ የሰው ልጅች በማለዘብ ለማሞኞች ተባባሪ እየሆንክ ነው።
ምድርን በሽብር
ወደ ገሃነም የቀየርዋት ኢሉሚናቲዎች
ተረት ተረት የሚመስላችው ስዎች
ገና ከእንቅልፋቸው ያልነቁና የሰይጣን
ማህበርተኞችን ድብቅ አላማ
ማስፈጸምያ በመሆን ላይ
ናችው።አገሮችን በሴራቸው በመበጥበጥ
የቆዩት ኢሉሚናቲዎች አሁን
ደግሞ ዋነኛ ጠላታችን ብለው
የሚያስብዋት የቃልኪዳን ምድር
ኢትዮጵያን ለማሸበርና የመጨረሻ
ዕቅዳቸውን የሆነውን አንድ
የዓለም ስርዓት(New World
Order)- የአውሬው-666-መንግስት ለመመስረት መንገድ ላይ ናቸው።ትንቢት ከመፈጸም አይቀርምና።ጠላታችን የስማዝያ
ጭፍሮችና የተጣሉት የኢሉሚናቲ
መንፈስ ናቸው።ታድያ ጊዜው የምንነቃበትና
የምናነቃበት እንጂ በፌዝና በቧልት ራሳችንን የሴራቸው ሰለባ አድርገን ነፍሳችንን ለጥንተ ጠላታችን ዲያብሎስ የምናስረክብበት አይደለም።
ሚያዝያ 25,2009 ዓመተ ምሕረት