ዘርአዳዊት ዘ-ኢትዮጵያ
የሃገረ እንግሊዝ ዜግነት ያላት ጸሓፊ፣የሴቶች መብት ተሟጓች፣የወሊድ ቁጥጥር ጀማሪ ማሬ ቻርሎተ ካርሚካኤል ስቶፐስ በመላው አለም በሰነ ተዋልዶ ጤና የሚሰራውን የማሪ ስቶፕስ ክሊኒክ መስራች ነች።ይህ በስምዋ የተሰየመው አለም አቀፍ ድርጅት በሃገራችን ኢትዮጵያም የሚሰራ ነው።በግል ካጠናህዋቸው ማሪ ስቶፐስ በአገራችን ከሚሰራቸው ስራዎችም የቤተሰብ ምጣኔ ፣እርግዝናን መከላከል(contraceptive methods) እና የእርግዝና ውርጃ(abortion ) ዋናወቹ ናቸው።ይህንን ጸረ የሰው ልጅ የሆነውን ሰይጣናዊ ስራ "ስለምናስብልዎ" በሚል የሽፋን ቃል በመጠቀም በመገናኛ ብዙሃን በመስበክ በህዝብ ላይ የጭንቅላት ቁጥጥር ሴራ በመዘርጋት በህዝቡ ላይ ሴሰኝነትና የፈጣሪን ስራ መቃወም የሆነዉን ውርጃ እንዲፈፅም ምቹ መንገድ ፈጥሯል።ፈጣሪ የሰው ልጅ ዘሩን እንዲተካበት የሰጠውን ወሲብ የእርግዝና መከላከያዎችን በመተማመን ወሲብን አላግባብ እንዲጠቀምበት አድርጓል።"ብዙ ተባዙ ምድርንም ምሉአት።"ዘፍ ፩፤፳፰ የሚለዉን የእግዚአብሐርን ቃልም መቃወም ይሆናል።ይህም የአለም ቁንጮዎቹ ኢሊሙናቲዎች ካላቸው ድብቅ አንድ የአለምን መንግስት የመመስረት አጀንዳ በቀጥታ ይያያዛል።ምስጥራዊ በሆነውና ማን እንደተከለው በማይታወቀው እቅዳቸውን በሚገልጸው የጆርጅያ ትክል ድንጋይ(Georgia
guidestones) ላይ ተጽፈው ካሉት መመርያዎችና ዕቅዶች አንዱ ስለ ሰነ ህዝብና የወሊድ ቁጥጥርን ይገልፃል።የአለም ህዝብን የወሊድ ሁኔታ በመቆጣጠርና የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ማለትም ተላላፊ በሽታዎችንና ክትባትን በመዘርጋት የአለምን ህዝብ ወደ 500 ሚልዮን በማውረድ ሰይጣናዊ የሆነውን አንድ የአለም መንግስት ለመመስረት ያላቸውን ዕቅድ ለመተግበር መንገድ ይጠርግላቸዋል።