EAR

አዲስ ነገር

Monday, 20 June 2016

የዓለም ጤና ድርጅትና ዶክተር ቴዎድሮስ አድሓኖም

ዘርአዳዊት -ኢትዮጵያ

ሰላቢ እጆች (illuminati) የአለም ህዝብ ለመቆጣጠር በሚያደርጉት ጉዞ በተቻላቸው አቅም ወሳኝ የሆኑ የአለማችን ድርጅቶች መቆጣጠር ይሞክራሉ።እስከ አሁን ድረስም ለድብቅ አጀንዳቸው ማስፈጸምያ የተመሰረተው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት(United Nations) ነው።ይህ ድርጅት ስያሜው የአለም መንግስታት ያቀፈ ይምሰል እንጂ የጥቂት ሴረኞች ሰዎች አላማ ማስፈጸምያ ነው።ይህንን ለማረጋገጥ ድርጅቱ በተግባር የሰራቸው ተጨባጭ ስራዎች ማጥናት ይቻላል።የዚህ ድርጅት አካል የሆነው የአለም ጤና ድርጅት (World Health Organization) አንዱ ነው።የአለም ጤና ድርጅት የአለም ህዝብ ጤና ለማስጠበቅ የተመሰረተ ነው ቢሉም እውነታው ግን በተቃራኒው ባላቸው የአለም ህዝብ ቁጥር የመቀነስ አላማ ድርጁቱ ለሴራ ማስፈጸምያ ይጠቀሙበታል።
ይህ ድርጅት አዲስ የሚመራው ግለ ሰብ ለመምረጥም በሂደት ላይ ነው።እጩ ሆነው ከተመረጡት ግለሰቦች አንዱ ኢትዮጵያዊው ግለሰብ ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ናቸው።ዶክተሩ ይህንን ድርጅት ለመምራት እንደሚመረጡ እርግጠኛ ነኝ።ሰላቢ እጆች(illuminati) ቅዱስት ምድር ኢትዮጵያ ዋነኛዋ ትኩረታቸውና የሴራ አላማቸው ነች።ምክንያቱም ቅዱስ የሆነው ጥበብዋና የእግዚአብሔር ቃልኪዳን ያላት ምድር በመሆንዋ ነው።ታድያ ጊዜው ደርሶ በሚልኳቸው አገልጋዮችና በማወቅም ባለማወቅም የማህጸንዋ ልጆች በመጠቀም ሰይጣናዊ አላማቸው ለማስፈጸም ይሮጣሉ።
ሰላቢ እጆች የሰው ልጅ ከሚቆጣጠሩበት መንገዶች አንዱ የክትባት ኬሚካሎች ለህጻናትን በመስጠት ነው።ይህንን ከሚያስፈጹሙ ግለሰቦችና ድርጅቶችም አንዱ የቱጃሩ ቢል ጌትናስ ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንደሽን ነው።ይህ ድርጅት በአለም ዙርያ ስንት ህጻናት የሚቀመስ ምግብ አጥተው ሂወታቸው ሲያጡ ሰምቶ እንዳልሰማ አይቶ እንዳለየ በማለፍ በክትባት ሰበብ ተጨማሪ ህጻናት ለማኮላሸትና ለመግደል አድገዉም ትክክለኛ የአእምሮ እድገት እንዳይኖራቸው በማድረግ መና የሚያስቀር ድርጊት በበጎ አድራጎት ሽፋን ይሰራል።የቢል ጌት ስና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንደሽን በሃገራችን ኢትዮጵያ በዶክተር ቴዎድሮስ በድርጅታቸው ህወሓት ተባባሪነትና ፍቃድ እንደሚንቀሳቀስ ይታወቃል።ቢል ጌትስ የአለም ህዝብ ለመቀነስ ሆን ተብሎ የተለቀቀው የኢቦላ ቫይረስ የባለቤትነት ማረጋገጫ (patent) ባለቤት መሆኑ የሴራው ጫፍ አመላካች ነው።ይህንንና ሌሎች ብዙ ክፉ ስራዎች ያስተባበረው ዶክተር ቴዎድሮስ ለሰላቢ እጆች ለዋለላቸው ውለታ አለም ጤና ድርጅት ከፍተኛው ስልጣን እንደሚሰጡት ምንንም ጥርጥር የለዉም።
የህ.ወ.ሓ.ት መንግስት የቅድስት ሃገር ኢትዮጵያ ቀጥተኛዋ የተዋህዶ እምነት በማጥፋት በተሃድሶና በሌሎች እንቅስቃሴዎች የመናፍቅ (protestant) መናኻርያ ለማድረግ ባለው ሰይጣናዊ ዕቅድ በ2008 ዓመተ ምሕረት ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት 50,000 የፕሮቴስታንት አብያተ ክርስትያን ለመገንባት ባቀደው የደቡብ ባፕቲስት ፕሮቴስታንቶች የኢትዮጵያ ስጋዊው መንግስት የርዕሰ ስልጣን ባለቤቶች ፍቃድ ሲሰጥዋቸውና ሲያነጋገርዋቸው አንዱ ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ነበሩ።





የካቲት 13, 2008 ዓመተ ምሕረት