EAR

አዲስ ነገር

Wednesday, 31 August 2016

የኢትዮጵያ የቀን አቆጣጠር

·         ዘርአዳዊት -ኢትዮጵያ

ሃገራችን ሃገረ እግዚአብሔር ኢትዮጵያ ከሌሎች ሃገሮች ለየት የሚያደርጋት ስርዓተችዋ የእግዚአብሔር ክብር የሚገልጡና የሚያስቀድሙ መሆናቸው ነው።ከነዚህ መካከልም የምትጠቀምበትት የቀን አቆጣጠር አንዱ ነው።በቀጥታም የወሮቹ ስያሜ የእግዚአብሔርን ክብር የሚያጎሉ ናቸው።የምዕራባውያን የወሮችና የቀን ስያሜ ግን ከዚህ በተቃራኒ የጣኦት አምልኮ የሚገለጽባቸውና በቀጥታ ከአምልኮው ጋር የሚገናኙ ናቸው።ከአራት አመት በፊትም የካቶሊክ ቤተክርስትያን ፖፕ ፍራንሲስ የኢትዮጵያ የቀን አቆጣጠር ትክክለኛው አቆጣጠር መሆኑ መስክረው ነበር።የካቶሊክ ቤተክርስትያን  የዲያብሎስ (ኢሉሙናቲ) ባርያ መሆንዋ ይታወቃል።
የኢትዮጵያ የወቅቶች መቀያየር ራሱ የኢትዮጵያ የቀን አቆጣጠር ምስክር ነው።አሮጊት አመት አልቆ አዲስ አመት ሲገባ የሚታየው የወቅት ለውጥና የእንቁጣጣሽ አበባ በየቦታው መመልከት ተፈጥሮም ምስክር መሆንዋ ማረጋገጫ ነው።

    በመቀጠል የኢትዮጵያና የምዕራባውያን የቀኖችና የወር ስያመዎች ትርጉማቸው እናያለን።

 የቀኖች ስያሜ ትርጉም

 1.እሑድ - እሑድ፣ እሒዶት ከሚለው ንዑስ አንቀጽ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም አንድ አደረገ (የመጀመሪያ ሆነ) ማለት ነው፡፡ በዚህ ቀን ፍጥረታት መፈጠር ስለጀመሩ እሑድ ተብሏል፡፡
2. ሰኑይ - ሰኑይ፣ ሰኑዮት ከሚል ንዑስ አንቀጽ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም ሁለት አደረገ ማለት ነው፡፡ ለሥነ ፍጥረት ሁለተኛ ስለሆነ ሰኑይ (ሰኞ) ተብሏል፡፡
3.ሠሉስ - ሠልሶ፣ ሠልሶት ከሚል ንዑስ አንቀጽ የተገኘ ሲሆን ሦስት አደረገ ማለት ነው፡፡ ማግሰኞ ማለት የሰኞ ማግስት ማለት ነው፡፡ ሦስት መባሉም ለሥነ ፍጥረት ሦስተኛ ቀን መሆኑን የሚያስረዳ ነው፡፡
4. ረቡዕ - ረብዓ፣ ረብዖት ከሚል ንዑስ አንቀጽ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም አራት አደረገ ማለት ነው፡፡ ይኸውም ለሥነ ፍጥረት አራተኛ ቀን መሆኑን የሚያስረዳ ነው፡፡
5.ኀሙስ - ኀምሶ፣ ኀምሶት ከሚል ንዑስ አንቀጽ የተገኘ ሲሆን አምስት አደረገ ማለት ነው፡፡ ይኸውም ለሥነ ፍጥረት አምስተኛ ቀን መሆኑን የሚያስረዳ ነው፡፡
6.ዐርብ - ዐሪብ፣ ዐሪቦት ከሚል ንዑስ አንቀጽ የተገኘ ሲሆን ተካተተ ማለት ነው፡፡ ፍጥረታት እሑድ መፈጠር ጀምረው ዓርብ መካተታቸውን (ተፈጥረው መፈፀማቸውን) የሚያስረዳ ነው፡፡
7. ቅዳሜ - ቀዲም፣ ቀዲሞት ከሚል ንዑስ አንቀጽ የተገኘ ሲሆን ሰንበተ ክርስቲያን ከሆነችው ከዕለተ እሑድ ቀድማ ስለምትገኝ ቀዳሚት ሰንበት (ቅዳሜ) ተብላለች፡፡

የምዕራባውያኑ የቀናት ስያሜ ግን መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ስለሌለው ትርጕማቸው ለጣዖታት መታሰብያ የተሰጠ ነው፡፡ ይኸውም እንደሚከተለው ነው፡፡

1.  ጹንዳይጹን ዻይ የፀሐይ ቀን፣ ፀሐይን የሚያመልኩ ስለሆነ ለአምላካቸው የሰጡት የመታሰብያ ቀን፤ 
2.  ሞንዳይሞኦን ዻይ የጨረቃ ቀን፣ ጨረቃን የሚያመልኩ ሰለሆነ ለአምላካቸው የሰጡት የመታሰብያ ቀን፤
3.  ጡአስዳይጢኡ ዻይ የቲው ቀን፣ ቲው (የጦርነትና የጠፈር አምላክ) ለሚሉት ጣዖት የተሰጠ የመታሰብያን ቀን፤
4.Wአድነስዳይ – Wኦደን ዻይ የወደን ቀን፣ ወደን (የአደን አምላክ) ለሚሉት ጣዖት የተሰጠ የመታሰብያ ቀን፤
5.  ጥሁርስዳይጥሆር ዻይ የቶር ቀን፣ ቶር (የመብረቅ አምላክ) ለሚሉት ጣዖት የተሰጠ የመታሰብያ ቀን፤
6. ፍሪዳይፍረያ ዻይ የፍረያ ቀን፣ ፍረያ (የፍትወትና የውበት አምላክ) ለሚሉት ጣዖት የተሰጠ የመታሰብያ ቀን፤
7.  ጻቱርዳይጻቱርን ዻይ የሳተርን ቀን፣ ሳተርን (የእርሻ አምላክ) ለሚሉት ጣኦት የተሰጠ የመታሰቢያ ቀን ነው፡፡


የወሮች ስያሜ ትርጉም                 
1.መስከረም    ከረመ  ከረመ፥ ምሴተ ክረምት፣ የክረምት መካተቻ
         
2.ጥቅምት  ጠቀመ    ጠቀመ፥ ጽጌ መደብ አድርጎ ፍሬ ሲሰጥ
         
3.ኅዳር      ኀደረ       አደረ፥ ገበሬ አዝመራዉን ሲጠብቅ ከዱር ስለሚያድር
         
4.ታኅሳስ   ኀሠሠ      ፈለገ፥ መረመረ፣ ሰብአ ሰገል ጌታን ፍለጋ በኮከብ እየተመሩ መምጣታቸውን የሚያስረዳ ፨ማቴ።፪፡፩፡፯፨፡፡
                  
5.ጥር       ጠየረ      መጠቀ፥ ረዘመ፣ ከጥቅመ ሰናዖር ጋር የተያያዘ ነው ፨ዘፍ።፩፩፡፩፡፩፩፨፡፡
         
6.የካቲት   ከተተ      ሰበሰበ፥ ገበሬ ምርቱን መሰብሰቡን የሚያስረዳ፡፡
         
7.መጋቢት መገበ      መገበ፥ የመዓልትና የሌሊት ምግብና ትክክል (እኩል) መሆኑን የሚያስረዳ ነው፡፡
                  
8.ሚያዝያ  መሐዘ     ሚዝት ፈለገ፤ የሚዛዝት (የሚዜዎች) ወራት፤ ወሩ ጋብቻ ስለሚበዛበት የተሰጠው ስያሜ፡፡
         
9.ግንቦት   ገነባ        ገነባ፥ የባቢሎን ግንብ ሳይወር ሁለቱ መቅደሶች በዚህ ወር መመሥረታቸውን የሚያስረዳ ፨፫ነገ።፮፡፩፣ ዕዝ።፫፡፰፡፩፩፨፡፡
                  
10.ሰኔ        ሠነየ        አማረ፥ የማሣው በዘር መሸፈኑን የሚያስረዳ ነው፡፡
                  
11.ሐምሌ    ሐምለ     ለመለመ፥ ወሩ የቅጠላቅጠል፣ የልምላሜ ወር መሆኑን የሚያስረዳ
                  
12.ነሐሴ     ነሐሰ       ሠራ፥ ጨረሰ፣ የመጨረሻ ወር
                  
በምዕራባውያኑ ግን መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ስለሌለው የወራቱ ስያሜ እንደ ቀናቱ ሁሉ ለጣዖታት መታሰብያ የተሰጠ ነው፡፡ ይኸውም እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
1.ጃኑኣርይጃኑስ ሞንጥ የጃኑስ ወር፣ የኆኀት (የደጅ) አምላክ ተብሎ ለሚታሰብ ጣዖት፤
2.ፈብሩኣርይፈብሩኣ ሞንጥ የፌብሯ ወር፣ ሥርየትን የሚሰጥ አምላክ ተብሎ ለሚታሰብ ጣዖት፤
3. ማርጭማርስሞንጥ የማርስ ወር፣ የጦርነት አምላክ ተብሎ ለሚታሰብ ጣዖት፤
4.ዓፕሪልዓጵሮዲተ ሞንጥ የአፍሮዳይት ወር፣ የፍትወትና የውበት አምላክ ተብላ ለምትታሰብ የሴት ጣዖት፤
5. ማይማኢኣ ሞንጥ የማያ ወር፣ የስጦታ አምላክ ተብላ ለምትታሰብ ጣዖት፤
6.ጁነጁኖ ሞንጥ የጁኖ ወር፣ የጋብቻና ሴቶችን ጥሩ እንዲሆኑ ታደርጋለች ተብላ ለምትታሰብ ሴት ጣዖት፤
7.ጁልይጁሊኡስሞንጥ የጁሊዮስ ቄሳር መታሰብያ ወር፤
8.ዓኡጉስትዓኡጉስቱስሞንጥ የአውግስጦስቀ ቄሳር መታሰብያ ወር፤
9.ጸፕተምበርጸፕተም ሰፕተም፣ ሰባት፣ ሰባተኛ ወር፤

10. ዖችቶበርዖችቶ ኦክቶ፣ ስምንት፣ ስምንተኛ ወር፤
11. ኞቨምበርኞቨም ኖቨም፣ ዘጠኝ፣ ዘጠነኛ ወር፤

12.ዸቸምበርዸቸም ዴሰም፣ ዐሥር፣ ዐሥረኛ ወር በማለት ወራቱን በሙሉ እንደ ቀናቱ ሁሉ ለጣዖታት መታሰብያ አድርገው ይጠሩዋቸዋል፡፡