EAR

አዲስ ነገር

Monday, 19 December 2016

በዋልድባ ገዳም ላይ ህወሓት ያደረገው ምስጢራዊ ስብሰባ እና ገዳሙን ለማፍረስ ያደረጋቸው እኩይ ተግባራት

አለማችን ክፉዎችና በክህደት መጠጥ የሰከሩ ሰዎች እንዳልዋት ሁሉ ጥቂት ሰዎች ደግሞ ምንም ተጽዕኖ ሳያሸንፋቸው ለእውነት የቆሙ አሉ ከነዚህ አንዱ አቶ ገብረመድህን አርአያ ናቸው።አቶ ገብረመድህን አርአያ የህወሓት መስራች፣ የፖሊት ቢሮ አባል እና የፋይናንስ ኃላፊ የነበሩ አሁን በስደት በአውስትራሊያ ነዋሪ ናቸው።ህወሓት በዋልድባ ገዳም የሰራው ሴራ እንደሚከተለው ይነግሩናል።

የዋልድባ ገዳም በህዋሓት መሪዎች በዓይነ ቁራኛ የወደቀው ገና ትገሉ እንደተጀመረ ነው። የዋልድባ ገዳም የህወሓት መሪዎች እንዲወድም ሃሳብ ያቀረቡትበ፲፱፸፫ መጨረሻ አካባቢ ሲሆን፣ አቅማራ ተብሎ በሚጠራ ቦታ በውቅቱ የህወሓት መናኸሪያ ነበር። በተመቤን ውስጥ የሚገኘው ቦታ በፕሮፓጋንዳ /ቤትተሰብስበው ወሰኑ፤ በስብሰባ የነበሩት አመራር ፖሊት ቢሮው በሙሉ ነበር። እነሱም፣ ስብሃት ነጋ፣ አረጋዊ በርሄ፣ ገደይ ዘርአጽዮን፣ አባይ ፀሃየ፣ ስዩም መስፈንእና መለስ ዜናዊ ነበር። በወቅቱ /ኮሚቴ የነበሩ ናቸው።  Ato Gebremedhin Araya former TPLF leadership member


በዚህ ስብሰባቸው የዋልድባን ገዳም እጣ ፈንታ ወሰኑ። ዋልድባ እንዲወደም የወሰኑት በዚህ ስብሰባቸው ነበር። የዋልድባ ገዳም ለብዙ መቶ ዘመናት የቅዱሳን ብፁአን፣ ባህታውያን፣ ቀሳውስት፣ አባቶች፣ ደናግል፣ ዲያቆናት ወዘተ ሰፈር በመሆን በኢትዮጵያ ቅዱስና በታሪክ ትልቅ ምእራፍ የያዘ ገዳም ነው። ይህ ቅዱስገዳም የቅዱሳን ማረፊያ በመሆኑ በታላቅነቱ የሚታወቅ ነው። ገዳሙ የታነጸው በ፲፪ኛው ክፍለ ዘመን በብፁእ ወቅዱስ አቡነ ዮሴፍ ነው።ቅዱሳን ወደኢትዮጵያእንደገቡም ያረፉበት፣ የተሰባሰቡበት ቦታ እንደሆነ በርካታ አማንያን ይናገራሉ።ዋልድባ ገዳም ታሪካዊ ቅርሶች፣ የግዕዝ ብራና፣ ታላላቅ መጻሕፍት፣ ጥናታዊናታሪካዊ መዛግብት የሚገኙበት ስፍራ ነው።

የህዋሓት ሴራ በዋልድባ ገዳም ላይ
ከዚህ ቀጥየ የማቀርበው ፀረ ዋልድባ ገዳም የሆኑትን፣ ከላይ ስማቸው የተዘረዘረውን የህዋሓት ፖሊት ቢሮ መሪዎች በ፲፱፸፫ በአቅማራ፣ ተምቤን የወጠኑትን ፀረዋልድባ ሴራ ነው። በብዙ ታጋዮችየሚታወቅ፣ በይበልጥም ከፍተኛ የሕዝብ ግንኙነት መሪዎች፣ የስለላ ታጋዮች፣ የክፍል መሪዎች ወዘተ በትክክል የሚያውቁትሴራ ነው። በስብሃት ነጋ ተነግሮናል፣ ስለዚህ ድብቅ ምስጢር አይደለም።ለሕዝብና ለተራ ታጋይ ግን ድብቅ ምስጢር ነበር።
ከላይ የተጠቀሱት የህወሓት መሪዎች የዋልድባን ገዳም በተመለከተ ብዙ ከተነጋገሩበት በኋላ ሙሉበሙሉ ለማጥፋት በሚከተሉትን ምክንያቶች አድርገውወሰኑ፤

. በሰሜን ኢትዮጵያ የክርስትና መስፍፋት ዋና መሰረቱ በዋልድባ ገዳም እየተማሩ የሚወጡት ናቸው። በተለይ በትግራይ የሚገኙት አብያተ ክርስትያናትመሪዎች በዚሁ ገዳም የተማሩ ናቸው። ቀሳውስት፣ ዲያቆናት በዚሁ ገዳም የተማሩ ናቸው። ይህ ገዳም እያለ የክርስትና ሃይማኖት ከትግራይ ውስት ለማስወገድአይቻልም። ለወደፊቱ ከድል በኋል ለምናቋቁመው የትግራይ መንግሥት ትልቅ መሰናክል የሚሆኑት የእስልምና እና የክርስትና ሃይማኖቶች ናቸው። ስለሆነምዋልድባ ገዳም የክርስትና ሃይማንቶት መፈልፈያ ስለሆነ ከምንጩ ማድረቅ አለብን በማለት የህወሓት ፖሊት ቢሮ አባላት፣ማለትም፣ ስብሃት ነጋ፣ አረጋዊ በርሄ ግደይ ዘርአጽዮን፥ አባይ ፀሃየ፣ ስዩም መስፍን እና በወቅቱ /ኮሚቴ የነበረው መለስ ዜናዊ በገዳሙ ላይ ውሳኔ አስተለለፉ። ውሳኔውም፤
. በገዳሙ ተንቀሳቃሽ ንብረትና የማይንቀሳቀስ ንበርት ላይ ጥናት ማካሄድ፤
. የገዳሙ ሃላፊዎችን ስም ዝርዝር ማጥናትና ማሳወቅ፣
. የዋልድባ ገዳም ግምጃ ቤት ውስጥ የሚገኙትን ቅርሳ ቅርስ፣ ጥንታዊ መጽሐፍትና መዛግብት በዝርዝር ማጥናት፣
. የገንዘቡን ክምችትና ቦታውን አጥንቶ ማሳወቅ። ይህንን ሁሉ በረቀቀ ስለላ ማጥናትና መከታተል የፖሊት ቢሮው ሃላፊነት ይሆናል ተብሎ ተወሰነ።

ለዚህ ጥናት ወደ ዋልድባ ገዳም አስርገን የምንልከው ታጋይ ቢያንስ ቢያንስ የድቁና ማእረግ ያለው፣ የቤተክረስቲያን ትምህርት ያለውና ያጠናቀቀ ታጋይ መሆንአለበት በማለት የህወሓት አመራር በአቅማራው ስብሰባ ወሰኑ። በዚህ ስብሰባ ሃላፊነቱ የተሰጠው ለስብሃት ነጋና ለግደይ ዘርአጽዮን ነበር። ሁለቱ የፖሊት ቢሮአባላት፣ የህወሓት ሊቀመንበር እና /ሊቀመንበር ናቸው። በውሳኔው መሰረት ወደ ሥራቸው ተሰማሩ። ይህን የሥራ ሃላፊነት የተረከቡት የቤተ ክህነት ብቁእውቀት ያለው ሰው ማግኘት ካባድ ቢሆንባቸውም፣ በየዞኑ የሚገኙትን የሕዝብ ግንኙነት ታጋይ ሃላፊዎችን በማነጋግር በምስጢር ደብዳቤ በመላላክ ብዙ ጊዜፈጁ።

 ፲፱፸፬መጨረሻ አካባቢ በተምቤን አውራጃ ጣንቋ አበርገሌ ውስጥ የድቁና ማእረግ ያለው ብቁ ወጣት ዲያቆን ተገኘ። አበርገሌ ተወልዶ ያደገ፣ የቤተ ክህነትትምህርቱን ያጠናቀቀ ቀዳሽ ነው። ዘመናዊ ትምህርት የለውም። የዞኑ የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ የነበረውና አራት ጓዶቹን አሰባስቦ ድርጅታችን ህወሓት እናንተንለትግል ይፈልጋችኋል ተብለው ተገደው ወደ ወታደራዊ ማሰልጠኛ () ተላኩ። ይህ የቤተ ክህነት ድቁና ያለው ወጣት ልዩ ዳብዳቤ ለአስገደ ግብረስላሴተላከለት። በደብዳቤው የተካተተው ለልዩ ሥራ ስለሚፈለግ ጥሩ እንክብካቤ እንዲደረግለት የሚል ነበር። የ፪ አስልጣኞችም በተላከው ደብዳቤ መሰረትተንከባክበው ያዙት። የአንድ ወር ወታደራዊ ትምህርቱን አጠናቀቀ።ይህ ታጋይ በርሄ መብራህቱ ይባላል።

በርሄ መብራህቱ ከማሰልጠኛው ጣቢያ አስወጥተው ሰው በማያገኘው አንድ ገበሬ ቤት ደበቁት። በዚሁ ድብቅ ቦታ የሚገናኘው ከኪሮስ ሃይለ (ወዲ ሃይለ) ጋርብቻ ነበር። ኪሮስ ሃይለ የወታደራዊ ማሰልጠኛ አስትዳዳሪ ሃላፊ ነው። አስፈላጊ እንክብካቤም አደረገለት። ከአስር ቀናት በኋላም ካንድ ትልቅ አመራር ጋርእንደሚገናኝ ነገረው። ከማንም ሰው ጋር እንዳይገናኝ አስጠነቀቀው። እንዲሁ እያለ ከ፲፫ ቀናት በኋላ ስብሃት ነጋ መጥቶ እዛው ድብቅ ቤት ተገናኙ። ስብሃት ነጋናበርሄ መብራህቱለ፱ ቀናት አብረውት በመቆየት ስብሃት ታጋይ ዲያቆን በርሄ መብራህቱ ወደ ዋልድባ ገዳም ለስለላእንደሚላክና እገዳሙ ወስጥ ገብቶ የስለላጥናቱን እንደሚያካሂድ፣ ምን ምን መስራት እንዳለበት አሰለጠነው። የሚፈጸሙትን ተግባራትም በዝርዝር አስጠናው። ከሚፈጽማቸው ተግባራት መካከል፣በዋልድባ ገዳም ያሉትን ጥናታዊ ቅርሶች፣ የብራና መጻህፍት፣ መዛግብት፣ የገዳሙን የሚንቀሳቀስና የማይንቀሳቀስ ንብረት፣ ዋና ግምጃ ቤቱ ወስጥ ያለውን ወርቅወዘተ የሚቀመጥበትን፣ የዋልድባ ገዳም ሃላፊዎችን ስም ዝርዝር፣ ቀሳውስት፣ ዲያቆናትና ሌሎች አስፈላጊ ናቸው የምትላቸውን ስም ማሳወቅ ወዘተ ተብሎተነገረው። ይህንን ጥናት ወደኛ ለማስተላለፍ ጥሞናና ጊዜ የሚጠይቅ ሥራ መሆኑን ማወቅ አለብህ። መኖሪያህ ገዳሙ ውስጥ ነው። ቀናት የፈጀ ገለጻውንትምህርቱን ሲጨርስ ከሳምንታት በኋላ እንገናኛለን ተባለ። ግደይ ዘርአጽዮን መጥቶ ያነጋግርሃል በማለት ለጊዜው ተሰናበተው። ግደይ ዘርአጽዮን ከሁለት ቀንበኋላ ወደ ወታደራዊ ማሰልጠኛ በመሄድ ኪሮስ ሃይለን በማግኘት ኪሮስ ሃይለም ታጋይ በርሄ መብራህቱን ወደተደበቀበት ቦት ይዞ በመሄድ አገናኘው። ግደይምለቀናት ታጋይ በርሄ መብራህቱን ስለ ስለላ ሥራው አሰለጠነው። መገናኛው የምስጢር ቃል ኮድ መሆኑን አስረግጦ አስተማረው። ከማን እንደሚገናኝ፣ የምስጢርኮዱ ስብሃት ተመልሶ ስለሚገናኝህ ይነግርሃል በማለት ተሰናበተው።

ስብሃት ነጋ ከሳምንት በኋላ ተመልሶ መጣ። ሲመጣም በቀረጢት የተቋጠሩ እቃዎችን ይዞ መጣ። ከረጢቱን ፈትቶ ለታጋይ በርሄ መብራህቱ አሳየው፤ መስቀል፣የቄስ ጥምጥምና ቆብ፣ የቄስ ዘንግ፣ መቁጠሪያ፣ ጭራ፣ ሙሉ የቄስ ልብስ፣ ጋቢ ወዘተ ለአንድ ቄስ የሚያስፈልገውን ሁሉ በተሟላ ሁኔታ ሰጠው። ታጋይ በርሄመብራህቱም የመጣለትን ተረከበ። ከአሁን በኋላ ስምህ አባ ገብረሥላሴ ነው። ዋልድባ ገዳም ስትገባ አባ /ሥላሴ መሆንህን አስተዋውቅ። በርሄ መብራህቱንእርሳው ተባለ፣ በጉዳዩም ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጠው። ከኔም ሆነ ከግደይ ዘርአጽዮን ጋር የምትገናኝበት የምስጢር ኮድ ይህ ነው ብሎ ሰጠው። የሚላኩልህንመልእክቶች ተቀበል፣ የተሳሳተ ኮድ ከሆነ አትቀበል፣ የሚመጣውን ሰው ሁሉ አታነጋግር ተባለ። ከአንተ ጋር የሚገናኘው ብስራት አማር ብቻ ነው። ሲመጣአስተዋውቅሃለሁ። በዓመት ሁለት ጊዜ ብቻ ትገናኛላችሁ። የተገኘውን ምስጢር ሁሉ ጽፈህና አሽገህ ትልክልናለህ። ከኔም ሆነ ከግደይ በዓመት አንድ ጊዜ ብቻበምስጢር በአካል በደብቅ ቦታ እንገናኛለን ተብሎ መመሪያ ተሰጠው።

አሁን የለበስከውን ልብስ ለብሰህ እስከ ተከዜ ትሄዳለህ። ተከዜን ከተሻገርክ በኋላ የለበስከውን ልብስ አውልቀህ ሙሉ የቄስ ልብስህን ትለብሳለህ። የዱሮውልብስህን ተመልሰህ እኛን ለመገናኘት ስትመጣ የቄስ ልብስህን ደብቀህ የዱሮ ልብስህን ለብሰህ እንገናኛለን። ሰው በማያገኘው ጥሩ ቦታ ደብቀው ተባብለውበዚሁ ተለያዩ። አባ /ሥላሴም ዋልድባ ገዳም ገቡ። ታጋይ በርሄ መብራህቱ (አባገ/ሥላሴገዳም ገብተው ሰፈሩ። ከ፲፱፸፭ እስከ ሐምሌ ፲፱፹፭    ዓመታት ዋልድባ ገዳም የኖረው ታጋይ በርሄ መብራህቱ ሰላዩ በዋልድባ ገዳም የሚታወቀው አባ /ሥላሴ ሲሆን የተሰጣቸውን የስለላ ተግባር በተሳካ ሁኔታቀጠሉበት። በዋልድባ ገዳም አባ /ሥላሴን የሚያውቋቸው የገዳሙ አባላት በርካታ ናቸው። ቢሆንም፣ ገዳሙን ለማጥቃት በህወሓት የተላኩ ሰላይ መሆናቸውንግንአያውቁም። ስምንት ዓመት በገዳሙ ሲኖር ማንነቱ እንዳይታወቅ በጥንቃቄ የኖረ ሰላይና መልእክተኛ ነው። ታጋይ በርሄ መብራህቱ (አባ /ሥላሴ)በዋልድባ ገዳም ባካሄደው የስለላ ጥናቱ ለስብሃት ነጋና ለግደይ ዘርአጽዮን በማስተላለፍ ዋልድባ ገዳምን ለካባድ ጥፋትና ውድመት የዳረገ ሰው ነው። ከግደይዘርአጽዮን በማለሊት ምስረታ ጉባኤ በሃሐምሌ ፲፱፸፯ ቢባረርም፣ ሰላዩን በተገቢው መንገድ አሰጥኖታል።

አባ /ሥላሴ (ታጋይ በርሄ መብራህቱ) በሚያስተላልፈው የስለላ መልእክቶች በብስራት አማረ እጅ በመላክ ለስብሃት ነጋና ለውውይት ለዘርአጽዮን ይደርሳል።ከዚሁ በመነሳት የሚፈለገውን ጥቃት ሁሉ በስምንት ዓመታት ቆይታው ገዳሙ ከሚጠቀምባቸው የምንጭ ውሃ እስከ እርሻ መሬት፣ በብዛት የጋማ ከብትናማንኛውንም ሃብት በዝርዝር አሳልፈው የሰጡና ያስተላለፉ ሰላይ ዛሬ ገዳሙ እየደረሰበት ያለው መፍትሄ የሌለው ውድቀትና ችግር የአባ /ሥላሴ (ታጋይ በርሄመብራህቱ) የስለላ ውጤቶች ናቸው። በወቅቱም ቢሆን በብስራት አማረ የሚመራው አፋኝና ሽብርተኛ ገዳይ ቡድን አድፍጠው በመጠባበቅ ብዙ ብፁአንአባቶችን፣ ቀሳውስቶችን፣ በርካታ ዲያቆናትን ደብዛቸውን አጥፍቷል። ሙታኖችን ገዳሙ ይቁጠራቅቸው። ለዚህ ሁሉ ወንጀል ተጠያዎቹ ስብሃት ነጋና ግደይዘርአጽዮን ናቸው።
ዛሬ በዋልድባ ገዳም ላይ እየደረሰ ያለው ጥፋትና ውድመት በስብሃት ነጋና በግደይ ዘርአጽዮን በታቀደ የስለላ መረብ ምክንያት ነው። በጠቅላላ ለጥንታዊውናባለታሪኩ ገዳም መውደም ተጠያዊዎቹ የህወሓት ከፍተኛ መሪዎች ናቸው። ለጥፋት ውሳኔው ዋናዎቹ ተባባሪዎች፣ አረጋዊ በርሄ፣ አባይ ፀሃየ፣ ስዩም መስፈን እናበወቅቱ የማእከላዊ ኮሚቴ አባል የነበርው መለስ ዜናዊ ናቸው። በዋልድባ ገዳም ዛሬ እየደረሰ ላለው ውድመት የገዢው ስርዓት ህወሓት ሙሉ ለሙሉ በሃላፊነትተጠያቂ ናቸው። ወንጄሎቻቸውም፤

. ታላቅና ባለ ታሪክ የሆነውን የዋልድባን ገዳም አውድመዋል፣
. ብዙ ብፁአን አባቶችን፣ ባህታዊያንን፣ ቀሳውስትን ገድለዋል፣ አጥፍተዋል፣
. የዋልድባን ገድም ጠቅላላ ሃብታና ንበረት ዘርፈዋል አስዘርፈዋል፣
. ጥንትዊ የብራና መጽሐፍት፣ የታሪክ መዛግብትን ወዘተ ዘርፈዋል፣ አስዘርፈዋል፣
. የገዳሙን ተንቀሳቃሽና የማይንቀሳቀስ ሃብትና ንብረት፣ የጋም ከብቶች፣ የእርሻ ቁሳቁሶችን ወዘተ በህወሓት ባለሥልጥናት በጉልበት ወስደዋል።

በሥልጣን ላይ ያለው ፋሽስትና ሽብርተኛ ህወሓት ኢትዮጵያን በቅኝ ግዛቱ ሰር ከጣላት ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በዋልድባ ገዳም እየደረሰ ያለው ፋታ የሌለውጥቃት ስብሃት ነጋና ግደይ ዘርአጽዮንበሸረቡት ተንኮል የዋልድባ ገድማ ጥፋት እንደቀጠለ ነው። ዛሬ የዋልድባ ገዳም በውድመት አፋፍላይ ተንጠልጥሎይገኛል። ክብሩና እና ህልውናው ተገፎ የባንዳዎችና የህወሓት አመራር የግል ንብረታቸው አድርገውታል።

የዚህ ቅዱስ ቦታ ጥቃትና ውድመት፣ ሃብታና ንብረት መዘረፍ፣ የብፁአን አባቶች ሕይወት መጥፋትወዘተ ተጠያቂው ህወሓት ነው። የዚህ ፋሽስትና ዘራፊመሪዎች ሁሉ ለቅዱስ ገዳሙ መጥፋት በሕግ ተጠያቂዎች ናቸው።